SNNPRS-BOSIT
የደቡብ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከዩኒቨርስቲዎች ጋር ባደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሠረት በቴክኖሎጂው ዘርፍ ለተግባር ልምምድ የሚላኩ ተማሪዎችን ተቀብሎ የተማሪዎችን ክህሎት በተግባር ስልጠና እያጎለበተ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
በዚሁ መሠረት ለተግባር ልምምድ /አፓረንት ሽፕ/ የመጡት የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተቋሙ በነበራቸው የይቆታ ጊዜ ሲያለሙት የነበረ የዳታ ቤዝ /የመረጃ ቋት/ የመጀመሪያ ዙር ግምገማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስርፀት ዘርፍና የቢሮው ም/ኃላፊ፣የስራ ክፍል ዳይሬክቶሬቶች እና ከፍተኛ የዘርፉ ባለሙያዎች የተገመገመና አስተያየት የተሰጠበት ሲሆን በሁለተኛዙር የግምገማ ሂደት ተማሪዎቹ የተሰጣቸውን አስተያየት እንደ ግብዓት በመጠቀም ተሻሽሎ የለማ የዳታ ቤዝ ሲስተም አቅርበው አስገምግመዋል፡፡
በቀጣይም ተማሪዎቹ በመልማት ሂደት ላይ የሚገኘውን ሲስተም ከፍጻሜ ለማድርስ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው እና ወደ ዩኒቨርሲቲያቸው ሲመለሱ ከመምህራኖቻቸው ጋር በመቀናጀት ጅምር…Read More
መስከረም 10/01/02015 ዓ. ም ግንባር ላይ እየተዋደቀ ለሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የመንግስት ሰራተኞችና አመራሮች የደረቅና ሰንባች ምግቦችን አዘጋጅተዋል።
በስንቅ ዝግጅቱ ወቅት ሰራተኞቹ የሀገሪቱ ሉኣላዊነት ተከብሮ አስተማማኝ ሰላም እስከሚሰፍን ድረስ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል ።
በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከዩኒቨርስቲዎች ጋር ባደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሠረት በክልሉ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች በቴክኖሎጂው ዘርፍ ለተግባር ልምምድ የሚወጡ ተማሪዎችን ተቀብሎ የተማሪዎችን ክህሎት በተግባር ስልጠና እያጎለበተ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሠረት ከሀምሌ 01/2014ዓ.ም ጀምሮ ለተግባር ልምምድ /አፓረንት ሽፕ/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተቀበላቸው ተማሪዎች ከፍተኛ የዘርፉን ባለሙያዎች በመመደብ ድጋፍ ሲያደርግላቸው ቆይቷ፡፡ በተግባባር ልምምዳቸው ወቅት ተማሪዎቹ እንድያለሙ የተሰጣቸውን የበጀት ማኔጅመንት ሲስተም ፕሮጀክት አጠናቀው አስገምግመዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በተቋሙ ከፍተኛ የሲስተም ባለሙያዎች አጠቃላይ ይዘቱ ተገምግሞ በጥንካሬ እና በጉድለት አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡ ተማሪዎቹም በቀጣይ የተሰጣቸውን አስተያየት እንደ ግብአት በመጠቀም ሲስተሙን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እና አገልግሎት ላይ እንዲውል ለማድረግ እንደ ሚሰሩ ገልጸው ተቋሙ ላደረገላቸው ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋና…Read More
ባላደጉ ሀገራት የኢኮኖሚ ውድቀት አንዱ ምክንያት ያላግባብ የሚባክን ጊዜ ነው ያሉት የደቡብ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ አንድ ጉዳይ ለማስፈፀም ሁለት ቀንና ከዚያ በላይ ጊዜን እናቃጥላለን ይህ ደግሞ ያለ ስራ ማሳለፋችን ብቻ ሳይሆን ለተጨማሪ ብክነትም እየዳረገን ነው ብለዋል።
ባለፈው አመት የደቡብ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ተቋማት ስራዎቻቸውን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ኢንዲሆን ለማድረግ ባደረገው ጥረት በክልል ፣ዞንና ወረዳ ተቋማት በኔትወርክ በማስተሳሰር እንዲሁም ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት የተሻለ ውጤት መመዝገብ ተችሏል ብለዋል።
ቴክኖሎጂን በትውልድ ውስጥ ለማስረፅ ቢሮው በክልሉ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የአይሲቲ ሴንተር ( የሳይንስ ከበባት)ለመክፈት ጥረት አድርጓል ያሉት አቶ ገብሬ ይህም አዲሱን ትውልድ ከቴክኖሎጂ ጋር ለማቀራረብ ያግዛል ብለዋል።
አዲስ አበባ፡ 19/01/2014፡- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ /ኢመደኤ/ እና የደቡብ ክልል የሳይንስ፣ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ በኢመደኤ በኩል የተገኙት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አንተነህ ተስፋዬ ኢመደኤ በዘርፉ ትልቅ አቅም እንደለው ገለጸው የደቡብ ክልል የሳይንስ፣ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮም ወቅቱ የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ ለመጠቀም እና የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ከኢመደኤ ጋር በጋራ ለመስራት መወሰኑን አድንቀዋል፡፡
በቀጣይም ቢሮው ደህንነቱ የተጠበቀ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ለመዘርጋት በሚያደርገው ጥረት ኢመደኤ የበኩሉን ኃላፊነት ይወጣል ሲሊ ዶ/ር አንተነህ ገልጸዋል፡፡
የደቡብ ክልል የሳይንስ፣ የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ በበኩላቸው መ/ቤታቸው ቀደም ሲልም ከኢመደኤ ጋር በሳይበር ደህንነት ዙሪያ በጋራ ሲሰሩ እንደነበር አውስተው የዛሬው ስምምነትም ይበልጥ…Read More
በዕለቱ በነበረው መድረክ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ዋና ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ የውይይት መድረኩ የተፈጠረው ጉድለታችንም ሆነ ስኬታችን የጋራ በመሆኑ በበጀት ዓመቱ ከነበሩ ስኬቶች መልካም ተሞክሮን ለመቅሰም እንዲሁም ከጉድለቶቻችን መሻሻልን ለማምጣት ሁሉም የተቋም ሠራተኛ ባለቤት በመሆኑ በቀጣይ በጀት ዓመት ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ ለሴክተሩ ግብ ስኬት የድርሻውን እንዲወጣ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል። በልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ከምባታ ካዌ የተቋሙ የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ሪፖርትና የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የተቋሙ ሠራተኞችም መድረኩ ተቋማቸውን በጥልቀት እንዲረዱና…Read More
Copyrights 2020. . All Rights Reserved.
Developed by SNNPRS-SCIENCE AND INFORMATION TECHNOLOGY BUREAU