• Call Us
  • +25146 2206572

የደቡብ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ላይ ከተቋም ሠራተኞች ጋር በሀላባ ሲካሄድ የነበረው የውይይት መድረክ ተጠናቋል።

gubaeበዕለቱ በነበረው መድረክ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ዋና ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ የውይይት መድረኩ የተፈጠረው ጉድለታችንም ሆነ ስኬታችን የጋራ በመሆኑ በበጀት ዓመቱ ከነበሩ ስኬቶች መልካም ተሞክሮን ለመቅሰም እንዲሁም ከጉድለቶቻችን መሻሻልን ለማምጣት ሁሉም የተቋም ሠራተኛ ባለቤት በመሆኑ በቀጣይ በጀት ዓመት ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ ለሴክተሩ ግብ ስኬት የድርሻውን እንዲወጣ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል። በልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ከምባታ ካዌ የተቋሙ የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ሪፖርትና የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የተቋሙ ሠራተኞችም መድረኩ ተቋማቸውን በጥልቀት እንዲረዱና በየዘርፋቸው የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ግንዛቤ የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

የ2013 በጀት ዓመት አፈፃፀም ከዚህ ቀደም ከነበረው በእጅጉ የላቀ መሆኑ ተገምግሟል።

በ2014 በጀት ዓመት ከዘንድሮ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መሥራት እንዳለብን የቢሮው ኃላፊ አሳስበው ለዚህም ስኬት ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ መልዕክት አስተላልፈው የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።