የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ/ት ሳይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ SNNPRS-BOSIT የቢሮው አጠቃላይ ገጽታ ባለፉት ዓመታት በክልላችን የሰላም፣ የዲሞክራሲና የልማት ተግባሮች ለማከናወን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተነደፈው በብቃት ሊያስፈጸም የሚችል አቅም የተሟላ ሊሆን ባለመቻሉ ከክልል እስከ ቀበሌ በአጠቃላይ የመንግስት መዋቅር የሚታየውን የማስፈጸም አቅም ችግሮችን ለመቅረፍ የአቅም ግንባታ ስትራቴጂዎችንና ፕሮግራሞችን የሚያስተባብርና በበላይነት የሚያስፈጽም ተቋማዊ አካል ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የክልሉን አስፈጻሚና ፈጻሚ አካላት ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 36/1994 እንደገናም ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 64/95 የአቅም ግንባታ ማስተባበሪያ ቢሮ ሆኖ ሲቋቋም የኢንፎርሚሸን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ከ15 የአቅም ግንባታ ፕሮግራሞች እንደ አንድ አቅም ግንባታ ፕሮግራም ተቀርጾ ሲተገበር ቆይቷል፡፡ Read More ራዕይ “በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት” ተልዕኮ ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡ ዕሴቶች በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣ የስራ ፍቅርና ትጋት፣ ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣ ለለውጥ በጋራ መስራት፤ ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤ ችግር ፈቺነት፤ የማይረካ የመማር ጥማት፤ ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣ ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣ ዓላማ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍን በማሳደግ ለፖለቲካዊ፣ ማኀበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያለውን አስተዋጽኦ በማጐልበት ክልሉን የፈጣን ልማትና ዕድገት ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ፤ Testimonial ኤጀንሲው እያሳየ ያለው እመርታ አበረታች ቢሆንም ዓለም በቴክኒሎጂ ወዴት እየሄደች እንዳለች በማጤን ሁላችንም በዚህ ዘርፍ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይኖርብናል፡፡ የቴክኖሎጂ ጉዳይ በ ኤጅንሲው ብቻ የሚተው ተግባር ባለመሆኑ እያንዳንዱ ተቋም የሚሰጠዉን ተልእኮ በመዉሰድ ከኤጀንሲው ጋር ተቀናጅቶ መስራትና መደጋገፍ እንደሚገባ አምኖ በጋራ መስራት ያስፈልጋል " አቶ ታምሩ ታፌ:- የክልሉ ፋ/ኢ/ል/ቢሮ ምክትል ኋላፊ ቴክኖሎጂን ከማዘመን አንፃር ተቋሙ በርካታ ነገሮችን መስራት ይጠበቅበታል፡፡ የወረዳኔት መስመሮችን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ለማስገባት ውዝፍ እዳዎች ተጠናቀው የሚከፈሉበትን አግባብ ማበጀት እና የኦላይን የንግድ ስረዓቱን የማዘመን ስራን በማሳለጥ ዓለም ወደምትጓዝበት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ጉዞ በመጓዝ የክልሉን ደረጃ ማሻሻል ያስፈልጋል፡፡" ወሮ አብነት በለጠ:- በንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የን/ም/ፋ/ዕ/መ/አስ/ዳይሬክተር ኤጀንሲው እያሳየ ያለው እምርታ የአመራር ቁርጠኝነት እና ቴክኖሎጂውን በክልላችን ለማሳደግ ያለዉን ተነሳሽነት የሚያሳይ ነው፡፡ ይህን መሰል መድረክ አዘጋጅተው ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ትላንት እና ዛሬ የደረሰበትን ደረጃ ጥልቅ በሆነ ትንታኔ ግንዛቤ እንድንጨብጥ በማድረጋቸው የኤጀንሲውን አመራሮች እናመሰግናለን፡፡ ስለሆነም በቴክኖሎጂው ዘርፍ ዓለም እየሄደበት ያለው ፍጥነት እኛ ከምንሄድበት ፍጥነት በእጅጉ ስለሚለያይ ፍጥነታችንን (አካሄዳችንን) በማሻሻል ዓለም ከደረሰበት ስፍራ መድረስ ይኖርብናል፡፡ እንዲህ አይነት መድረኮችን በመፍጠር ለሌሎች አካላት ልምድ መስጠት አስፈላጊ በመሆኑ አመራሩ ጠንክሮ መስራት ይኖርበታል፡፡ እኛም ከጎናችሁ ሆነን ተቀናጅተን መስራት በሚገባን ነገር ሁሉ አብረን እየሰራን ቴክኖሎጂውን የማዘመን ስራ እንሰራለን፡፡ " አቶ መኮንን ደስታ፦ በፐብልክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ምክትል የቢሮ ሀላፊ SNNPRS-Science and Information Technology Bureau 1 Head Office 17 Branches In Zones 7 Branches In Special-Weredas View All Locations